25/01/2025
===========
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰዓሊተ ምሕረት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ፀሐይ ቆሞስ አባ ኃይለ መለኮትን ከአስተዳዳሪነት ያገደው ለቤተ ክርስቲያን አስቦ ወይስ ለእጅ መንሻ? አባ ኃይለ መለኮት ከሥራ ለመታገዳቸው ምክንያት የሆነው ክስ የቀረበባቸው መቼ ነው?
አባ ኃይለ መለኮትን አግባብ ባለሆነ መንገድ ከዐባይ እና ከዳሸን ባንክ 47 ሚሊየን ብር ተበድረዋል የሚል ክስ ቀርቦባቸው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጉዳዩን የሚያጣራ ልዑክ የመደበ ሲሆን በወቅቱ የተመደበው ልዑክ ጉዳዩን ሲመረምር ቆይቶ ለሀገረ ስብከቱ ሪፖርት ያደረገ መሆኑ ይታወቃል።
ልዑካኑ ለሀገረ ስብከት ሪፖርት ያደረጉበት ጊዜ በትንሹ ከሦስት ወራት በፊት ነው። ሀገረ ስብከቱ በወቅቱ አስተዳዳሪውን ያላገደበት ምክንያት ወቅቱ ከዝውውርና ከቅጥር የሚገኘው እጅ መንሻ የሚያባርርበት ጊዜ እንደነበር የሚታወቅ ነው። አሁን ላይ ሀገረ ስብከቱ ዝውውርና ቅጥር ማድረግ ስለማይችል ለገንዘብ ማግኛ ሲል አገልጋዮችን ከሥራ ማገዱን ሥራው አድርጎ በመንቀሳቀስ የጀመረው ልክ ዝውውሩ ከታገደበት ጊዜ አንሥቶ ነው።
ለዚህ ነው ከወራት በፊት ምንም እንዳልተፈጠረ በማድረግ ትቶ ያለፈውን የአባ ኃይለ መለኮት ጉዳይ እንደ አዲስ ተመልክቶ በዛሬው ቀን ከስራ ያገዳቸው። አንዳንዶቹ በወቅቱ ለአፍ ማዘጊያ ከ1ሚሊየን በላይ ገንዘብ ከቤተ ክርስቲያን በማውጣት ለሀገረ ስብከቱ ሠራተኞች አከፋፍለዋል በማለት የካቴድራሉ አገልጋዮች ይከሳሉ።
ይህ በእንዲ እንዳለ ከፊሎችን ደግሞ ከሥራ ከምናግዳችሁና መላ ከምትሉ የትኛውን ትመርጣላችሁ በማለት በድርድር እንደሚሰሩም ተሰምቷል።
ስለዚህ የመልአከ ፀሐይ አባ ኃይለ መለኮት እግድ ለቤተክርስቲያን ታስቦ ሳይሆን አሁን ደግሞ እሳቸውን አንስቶ ቦታውን ለሌላ ሰው ለመሸጥ ታስቦ ነው ቀደም ሲል ያከፋፈሉት አንድ ሚሊየን ብር ከሦስት ወራት በላይ አገልግሎት በላይ የሚሰጥ አልሆነም።