የዜና ማዕዘን

የዜና ማዕዘን Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የዜና ማዕዘን, Dubai.

''ደፍረን እናውራ ይበቃል እንበል ''ሞት እምቢ!ለምርጫው ተሰብስበን እንፀልይ ሲሉ የነበሩ የሀይማኖት አባቶች በአርሲ ለሚሞ*ተው ኦርቶዶክስ ወገናችን ግን ያሉት ነገር የለም። ''በግፍ ለተገ...
03/06/2026

''ደፍረን እናውራ ይበቃል እንበል ''ሞት እምቢ!

ለምርጫው ተሰብስበን እንፀልይ ሲሉ የነበሩ የሀይማኖት አባቶች በአርሲ ለሚሞ*ተው ኦርቶዶክስ ወገናችን ግን ያሉት ነገር የለም።

''በግፍ ለተገደላችሁ ወገኖቻችን ፈጣሪ ነፍሳችሁን ይማረው! ይሄ ሕዝብ ግን እራሱ ላይ በአስር ጣቱ ፈርሟል? ደፍረን እናውራ ይበቃል እንበል ''ሞት እምቢ!''

ታሪኩ ጋንካሲ (ዲሽታ ጊና)

  !​በአንድ ሀገር ላይ የብዙኃን መገናኛዎች (ሚዲያዎች) ዋነኛ ሚና እውነትን ማውጣት፣ የሕዝብ ዕንባን ማበስና የደካሞች ድምፅ መሆን ነበር። ነገር ግን ዛሬ ላይ በሀገራችን የምናየው እውነታ...
03/06/2026

!

​በአንድ ሀገር ላይ የብዙኃን መገናኛዎች (ሚዲያዎች) ዋነኛ ሚና እውነትን ማውጣት፣ የሕዝብ ዕንባን ማበስና የደካሞች ድምፅ መሆን ነበር። ነገር ግን ዛሬ ላይ በሀገራችን የምናየው እውነታ ሚዲያዎቹ ራሳቸው የጭቆና እና የዝምታ መሣሪያ መሆናቸውን ነው።
​በዕለታዊ መረጃዎች ላይ በግልጽ እንደምናየው፣ የኦርቶዶክሳውያን ሕይወት መጥፋት፣ መገደልና መሳደድ የማይመለከታቸው የሚመስሉ በርካታ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች አሉ። ይህ ዝምታ ደግሞ በድንገት የመጣ ሳይሆን፣ ነገሩ ምን ያህል የተቀናጀ እና የታቀደ መሆኑን በግልጽ ያሳያል።

ከኃላፊነት የሸሹ "ብሔራዊ" እና የግል ጣቢያዎች ውርደት

​የመንግሥትና የብሔራዊ ዜና ማሰራጫዎች ዝምታ እንደ EBC እና ETV News ያሉ የሕዝብ በጀት የሚፈስባቸውና የሀገር "ብሔራዊ" መገናኛ የተባሉ ተቋማት፣ የኦርቶዶክሳውያን ደም ሲፈስ ትንፍሽ አለማለታቸው እጅግ የሚያሳፍር ነው። እንደውም አወቃቀራቸውና ዜናዎቻቸው ከፋና (Fana TV) ጋር ተዋህደው አንድ ዓይነት የፖለቲካ አጀንዳ ብቻ የሚያስተጋቡ ሆነዋል።

​የመዝናኛና የንግድ ጣቢያዎች ቸልተኝነት እንደ Kana TV, EBS, ARTS TV, እና አርትስ ያሉ ጣቢያዎች ከሕዝቡ ኪስ በሚሰበስቡት ማስታወቂያና ትርፍ እየኖሩ፣ ያ ሕዝብ ሲታረድ ግን እንደማይመለከተው የውጭ ሀገር ጣቢያ ሆነው መቅረታቸው የታሪክ ጠባሳ ነው።

​የክልል ሚዲያዎች መሸሽ እንደ Amhara TV, OBN, AMN እና Abbay TV ያሉ የክልል መገናኛዎች የራሳቸውን ሕዝብ ሰቆቃ ወደ ጎን በመተው የፖለቲካ ትረካዎችን ብቻ ማስቀደማቸው የሞራል ውድቀታቸውን ያሳያል።

​ለመሆኑ እነዚህ ጣቢያዎች ሊያፍሩ አይገባም? > ከአንድ ሃይማኖት ተከታይ በላይ፣ የሰው ልጅ ሕይወት በግፍ ሲጠፋ ዝምታን መምረጥ የጋዜጠኝነትን መሠረታዊ ሕግ የጣሰና የሕሊና ፍርድ የሚያሰጥ ተግባር ነው።

ለኦርቶዶክሳውያን የተሰጠ ትልቅ ትምህርት፡ መፍትሔው ከራስ ብቻ ነው!

​ይህ በግልጽ የምናየው የሚዲያዎች ጥምረት አንድ ትልቅ እውነት ያስተምረናል። ኦርቶዶክሳውያን ከእነዚህ ጣቢያዎች ፍትሕን፣ ርኅራኄን ወይም ሚዛናዊነትን መጠበቅ ማቆም አለባቸው።

​ራስን_በራስ_መቻል➠ የራስን ድምፅ ማጉላት የሚቻለው በራስ ተቋማት ብቻ ነው። ኦርቶዶክሳውያን የራሳቸውን ጠንካራና ዘመናዊ የሚዲያ አማራጮች መገንባትና መደገፍ የግድ ይላቸዋል።

​አለመደገፍ ➠ ለሕዝብ ስቃይና ሞት ደንታ የሌላቸውን፣ ሕይወታቸውን እንደ ተራ ክስተት የሚቆጥሩትን እነዚህን የቴሌቪዥን ጣቢያዎች አለማየትና አለመደገፍ የሞራል ግዴታ ነው።

​አንድነትን ማጠንከር➠ ጠላትም ሆነ ወዳጅ የሚዲያ ከበባ አድርጎ ዝምታን ሲመርጥ፣ ኦርቶዶክሳውያን እርስ በርስ ከመደጋገፍና መፍትሔውን ከራሳቸው (ከቤተክርስቲያናቸውና ከአንድነታቸው) ብቻ ከመጠበቅ ውጪ ሌላ አማራጭ የላቸውም።

እነዚህ ሚዲያዎች በታሪክ ፊት ዕፍረትን ተከናንበዋል። የሕዝብ ዕንባ ያላንቀሳቀሰው ሚዲያ የቆመው ለሕዝብ ሳይሆን ለራሱ ጥቅም ብቻ ነው። ስለዚህ ኦርቶዶክሳውያን ሆይ! ከእንግዲህ ወደነዚህ ጣቢያዎች አንገታችሁን አትደፉ፤ መፍትሔው በእጃችሁ፣ ድምፃችሁም በራሳችሁ አንድነት ውስጥ ነው!

በምስራቅ አርሲ በዜጎች ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ጥቃት ተከትሎ፣ ታዋቂው ኡስታዝ ያሲን ኑሩ ለተጎጂዎች ድምፅ በመሆን ጥልቅ ሐዘናቸውን ገልጸዋል።ምነው የተከበረው የሰው ልጅ ህይዋት እንዲህ እ...
03/06/2026

በምስራቅ አርሲ በዜጎች ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ጥቃት ተከትሎ፣ ታዋቂው ኡስታዝ ያሲን ኑሩ ለተጎጂዎች ድምፅ በመሆን ጥልቅ ሐዘናቸውን ገልጸዋል።

ምነው የተከበረው የሰው ልጅ ህይዋት እንዲህ እረከሰ ?!!!
♻️♻️♻️♻️♻️
ደመ*ና—ደም መና!!

በምስራቅ አርሲ በውድ ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመውን አሰቃቂ ጥቃት በመስማቴ የተሰማኝን ጥልቅና መሪር ሐዘን ለመግለፅ እወዳለሁ።

የብዝኃ ኃይማኖትና ብሔር ብሔረሰቦች እናት የሆነችውን ሀገራችንን ሰላም ለማናጋት፤ ለዘመናት የተገነባውን የሕዝቦች የእርስ በርስ የጠበቀ ትስስር ለመበጠስ፤ ብሎም የዜጎችን ነፍስ ለርካሽ ዓለማዊ ግባቸው ማሳኪያ ለመጠቀም ያሰፈሰፉ እኩያን በተደጋጋሚ እየፈፀሙት ያለውን ሀገር አጥፊ ድርጊት አጥብቄ እኮንናለሁ። አወግዛለሁም።

የሰውን ልጅ ክቡር ህይዎት የሚያጠፉና የሃገራችን ኢትዮጵያን ዕድገት የሚገታ እኩይ ተግባር ላይ ተሰማርተው በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች እየፈፀሙት ያለውን መጠነ ሰፊ ጥፋት የሚመለከተው አካል አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ የዜጎችን በሰላም ወጥቶ የመግባት ሰብዓዊ መብት ማረጋገጥ ይገባዋል።

በሰላም ወጥተው ስለመግባታቸው መተማመኛ የሌላቸውን ዜጎች ያቀፈች ሀገር ወደፊት የመራመድ ዕድሏ የቀጨጨ፣ የማደግ ተስፋዋ የመነመነ ነውና ስለ ሀገሬ ያገባኛል፣ ይመለከተኛል የሚል ሁሉ ‹ሀይ› ሊል ይገባል።

ከምንም በላይ ደሞ መሰል አስነዋሪ ድርጊቶችን እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም በሕዝቦች መካከል አለመተማመንን የሚዘሩ ኃላፊነት የጎደላቸው ግለሰቦች የጉዳዩን አደገኛነት ከግምት በማስገባት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡና ቆም ብለው እንዲያስቡ አበክሬ ለመግለፅ እወዳለሁ።

አላህ የተበዳዮችን እምባ እንዲያብስ፤ ለበዳዮችም የእጃቸውን እንዲሰጣቸውና ፍትሕን እንዲያሰፍንልን የበረታ ዱዓዬ ነው።

ሰላም ለሀገራችን!

(ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ል)

Via ኡስታዝ ያሲን ኑሩ

♦ይህም ይመዝገብ ፦ ቴዲ “ለምን ዳሳ ጣል ብሎ ዘፈነ?” ብለው ምድርን ያናወጡ  #ፓስተሮችና  #ዑስታዞች፣ የአርሲን ጭፍጨፋ  አልሰሙም ይሆን?!በምስራቅ  #አርሲ ሀገረ ስብከት በየጊዜው የሚ...
03/06/2026

♦ይህም ይመዝገብ ፦ ቴዲ “ለምን ዳሳ ጣል ብሎ ዘፈነ?” ብለው ምድርን ያናወጡ #ፓስተሮችና #ዑስታዞች፣ የአርሲን ጭፍጨፋ አልሰሙም ይሆን?!

በምስራቅ #አርሲ ሀገረ ስብከት በየጊዜው የሚገደሉ ኦርቶዶክሳውያን ቁጥር እየጨመረ ነው።

በገዛ ሀገራቸው በሰላም የመኖር መብታቸው የተነፈገው የአርሲ ኦርቶዶክሶች፣ አንዴ ከቀያቸው ሲፈናቀሉ፣ አንዴ ከቤታቸው ተለቅመው በጅምላ ሲጨፈጨፉ፣ “ይድረሱልን!” ብለው የሚያሰሙት ጩኸት ግን ሰሚ አጥቷል። ዛሬም የሚደርስላቸው ሳይኖር፣ ደማቸው በግፍ እየፈሰሰ ያለው የዘመናችን ሰማዕታት ሆነዋል።

ነገር ግን፣ በየእምነት ተቋማቱ ስር ተሰግስገው የፖለቲካ አጀንዳ ሲያራምዱ፣ በመቅደስና በምንበር ሊነገር የሚገባውን ቅዱስ ቃል ወደ ጎን ገፍተው የፓርቲ ርዕዮተ ዓለምና የምርጫ ቅስቀሳ ሲሰብኩ የነበሩ ሰባኪያን፣ “ለምን መንግሥታችን ተነካ?” ብለው ድምፃቸውን ያሰሙ እነዚያ ሰዎች፣ ዛሬ ግን የአርሲን ጭፍጨፋ አላዩም? አልሰሙም? ወይስ ለማየትና ለመስማት አልፈለጉም ?!

የንፁሃን ደም ሲፈስ፣ የወገኖቻችን ጩኸት ሰማይ ሲያደርስ፣ ዝምታ ገለልተኝነት አይደለም፤ አቋም ነው። ዛሬ የተመረጠው ዝምታ፣ ነገ በታሪክ ፊት የሚጠየቅ ከባድ ምላሽ ይኖረዋል። እናም ይህም ይመዝገብ!

ይድነቃቸው ከበደ

ወደ ካናዳ ሰራተኛ መላክ ተጀምሯል ?" ገንዘብ አስከፍለዋቸው ተበልተው የመጡ ሰዎች አሉ " - ሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴርኢትዮጵያውያንን ለሥራ እድል ተጠቃሚነት ወደ ካናዳ ለመላክ "ፊውቸር ፊ...
03/06/2026

ወደ ካናዳ ሰራተኛ መላክ ተጀምሯል ?

" ገንዘብ አስከፍለዋቸው ተበልተው የመጡ ሰዎች አሉ " - ሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር

ኢትዮጵያውያንን ለሥራ እድል ተጠቃሚነት ወደ ካናዳ ለመላክ "ፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል" ከተሰኘው ድርጅት ጋር የተፈረመውን ስምምነት ተከትሎ ዜጎችን መላክ እንደተጀመረ በማስመሰል በሚያጭረብሩ አካላት ገንዘብ የተጭበረበሩ ሰዎች መኖራቸውን ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

ሚኒስቴሩ፣ ከካናዳ "ቀረበልኝ" ባለው ጥያቄ መሰረት ወጣት ባለሙያዎችን ወደ ካናዳ ለሥራ ለመላክ ከድርጅቱ ጋር በቅርቡ ስምምነት መፈራረሙ ይታወቃል።

ባለሙያዎቹን ወደ ካናዳ ለማሰማራት በመንግስት ፈቃድ የተሰጠው ብቸኛው ድርጅት "ፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል" መሆኑንና ከካናዳ ኤምባሲ ውጭ የቪዛ ወኪል እንደሌለ ሚኒስቴሩ በስምምነቱ ወቅት መግለጹ ይታወሳል።

ይሁን እንጅ ስምምነቱ ከተፈጸመ በኋላ በርካቶች " ወደ ካናዳ እንልካችኋለን " በሚሉ አካላት የማይገባቸውን ገንዘብ እየከፈሉ እየተጭበረበሩ ናቸው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ ባለሙያዎችን ወደ ካናዳ መላክ ጀምራለች ? " እንልካችኋለን " በሚል ገንዘብ ስለሚያስከፍሉ አካላት ጥቆማ ደርሷችኋል ? ሲል በሚኒስቴሩ የውጪ ሀገር ሥራ ስምሪት የውል ምርመራ እና ማጽደቅ ዴስክ ኃላፊ አቶ በዛወርቅ ከተማን ጠይቋል።

አቶ በዛወርቅ " ወደ ካናዳ መላክ አልተጀመረም። ክፍያም የለም " ብለዋል።

" ስምምነት ተፈረመ እንጅ ወደ ካናዳ የሚልክ መንግስት የሚያውቀው እውቅና የሰጠው ኤጀንሲ የለም " ያሉት ኃላፊው፣ " ገና የመላክ ስራው አልተጀመረም፤ ሲጀመር መንግስት እከሌ የሚባል ኤጀንሲ ካናዳ ላይ ፈቃድ ወስዷል ብሎ ያሳውቃል " ሲሉ ተናግረዋል።

" በዚህ ወቅት መላክ ስላልተጀመረ የሚልከው ህገወጥ ነው፤ ህገወጥ ላይ የሚሳተፍ ማህበረሰብ መኖር የለበትም። ክፍያም የለውም። ግን አብዛኛዎቹ አስከፍለው 'እንልካችኋለን' ብለው ነው ማስታወቂያ የሚያሰሩት። ይሄ ስህተት ነው " ብለዋል።

እያጭበረበሩ ያሉ ድርጅቶች፣ የተጭበረበሩ ዜጎች እንዳሉ ፈትሸው እንደሆነ ማብራሪያ የጠየቅናቸው ኃላፊው፣ " ገንዘብ አስከፍለዋቸው ተበልተው ወደዚህ (ወደ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር) የመጡ ሰዎች አሉ። ከፌደራል ፖሊስ ጋር ሆነን ገንዘብ የተቀበሉ ሰዎች ላይ ክትትል እየተደረገበት ነው። ጥቆማዎችም ይመጣሉ " ብለዋል።

" ተጭበረበርን " ብለው ያመለከቱት ዜጎች ብዛት ስንት እንደሆኑ ስንጠይቃቸው ግን ቁጥራቸውን ከመግለጽ ተቆጥበዋል።

አቶ በዛወርቅ ከተማ ፥ ስምምነት ተፈረመ ማለት ባለሙያዎችን ወደ ካናዳ መላክ ተጀምሯል ማለት እንዳልሆነና ክፍያም እንደሌለው ገልጸው፣ ማህበረሰቡ ይህን እንዲገነዘብ አሳስበዋል።

ከካናዳ መንግሥት " 'ይሄን ስራ እንድትሰሩልኝ ባለሙያ ትልኩልኛላችሁ ወይ?' " የሚል ጥያቄ እንደቀረበላቸው ገልጸው፣ "መንግስትም 'አዎ፤ ባለሙያ አለን፤ እንልካለን የሚል ስምምነት ተፈራርሟል። ያ ማለት ግን መላክ ተጀምሯል ማለት አይደለም " ነው ያሉት።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

03/06/2026

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናችን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።

ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት እንደሚከተለው ነው፦

መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።››
(መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪)

በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው።

የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል።

በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።

በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት

24/11/2023

Address

Dubai

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የዜና ማዕዘን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share