15/03/2024
የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ በየመሰረታዊ ድርጅት ዉስጥ ከሚገኙ ሙስሊም ወንድምና እህቶች ጋር አፍጥር መርሀ ግብር ማካሄድ ጀመረ::
በቀን 06/072016 ዓ.ም በተደረገዉ የአፍጥር መረሀ ግብር የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ብልፅግና ወጣቶች ሊግ ፅ/ቤት ኃላፊ ወጣት ማቲያስ ጌታቸዉ የተገኙ ሲሆን ይህ የአፍጥር መርሀ ግብር ወድማማችነትንና እህትማማችን ከመፍጠሩ ባሻገር ጠንካራ ተቋምን የሚፈጥር በመሆኑ በሌሎች ወረዳዎችም መስፋት አለበት በማለት መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል። በተጨማሪም የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ 8 ብልፅግና ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ የሆኑት ወጣት ተማረ አየነዉ ይህ የአፍጥር መርሀ ግብር በወጣት ያሲን ቤት ይጀመር እንጅ በሁሉም መሰረታዊ ድርጅቶች ተጠናክሮ የሚቀጥል ነዉ ብለዋል።