28/05/2024
ቅዱስ ኤፍሬም የአገልጋዩን ልብ መለሰ!!
እጅግ ደስ የሚል ዜና ነው:: ዶ/ር ሰባስቲያን ብሮክ የሲሪያክ ጥናት ፕሮፌሰር ሲሆን ሶርያዊውን ሊቅ ቅዱስ ኤፍሬምን ለምዕራቡ ዓለም በማስተዋወቅና ለእኛም ብዙ የቅዱስ ኤፍሬም ድርሰቶችን ለማንበብ እንድንችል ትልቅ ዕድል የከፈተ በዚህ ክፍለ ዘመን ወደር ካልተገኘላቸው የClassic studies ሊቃውንት አንዱ ነበር:: የሶርያ ቤተ ክርስቲያን ላደረገው አስተዋጽኦ ከዚህ በፊት የክብር ሜዳይ ብትሸልመውም በሃይማኖቱ ግን ፕሮቴስታንት ነበረ:: ያገለገለው አምላክ የቅዱስ ኤፍሬምን ጸሎት ሰምቶ ሰባስቲያን ብሮክ አሁን በሶርያ ቤተ ክርስቲያን ጥምቀተ ክርስትናና ምሥጢረ ሜሮን ተፈጽሞለታል::
የእኛን አባቶች ጥንታዊ መጻሕፍት ሲተረጉሙ ሳይድኑ የቀሩ ብዙዎች ናቸውና በሰባስቲያም ብሮክ መመለስ ከመላእክት ጋር ደስ ይለናል::