Nifas silk Lafto Woreda 12 Communication Affairs Office

Nifas silk Lafto Woreda 12 Communication Affairs Office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Nifas silk Lafto Woreda 12 Communication Affairs Office, Addis Ababa.

ከምንነጣጠልበት ይልቅ በርካታ የምንደመርበት ጉዳይ ላይ በማተኮር  የጉባ ብስራቶችን መድገም ይገባል ፥አቶ መብራቱ ደሴላፍቶ፡ ጥር 1/2018፦ከምንነጣጠልበት ይልቅ በርካታ የምንደመርበት ጉዳይ...
09/01/2026

ከምንነጣጠልበት ይልቅ በርካታ የምንደመርበት ጉዳይ ላይ በማተኮር የጉባ ብስራቶችን መድገም ይገባል ፥አቶ መብራቱ ደሴ

ላፍቶ፡ ጥር 1/2018፦ከምንነጣጠልበት ይልቅ በርካታ የምንደመርበት ጉዳይ ላይ በማተኮር የጉባ ብስራቶችን መድገም ይገባል ሲሉ የክፍለ ከተማው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መብራቱ ደሴ ገለጹ።

በዛሬው ዕለት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ "የጉባ ብስራቶች የወል ትርክት ትዕምርቶች" በሚል መሪ ቃል 6ተኛው አብርሆት የኪነ-ጥበብ ምሽት በለቡ መብራት ኃይል ተካሂዷል።

በመርሀ ግብሩ ላይ የክፍለ ከተማው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መብራቱ ደሴ የክፍለ ከተማው አፈጉባኤ አቶ ወጋየሁ ኃይሉን ጨምሮ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም ከ13ቱም ወረዳዎች የተውጣጡ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና የጥበብ አፍቃሪያን ታድመዋል።

የኪነ- ጥበብ ምሽት መርሃ ግብሩን የክፍለ ከተማው ባህልና ኪነ- ጥበብ ጽ/ቤት ያዘጋጀው ሲሆን የጉባ ብስራቶችን በሌሎች የልማት ስራዎች ለመድገም የሚያስችል እንዲሁም ገዢ ትርክትን በስነ ጽሁፍ ስራዎች ለማስረጽ ያለመ መሆኑም ተመላክቷል።

በእለቱ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፍት የክፍለ ከተማው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አቶ መብራቱ ደሴ፥ከምንነጣጠልበት ይልቅ በርካታ የምንደመርበት ጉዳይ ላይ በማተኮር የጉባ ብስራቶችን መድገም ይገባል ያሉ ሲሆን ወጣቶች ከመታደም ባለፈ በውሳጣቸው ያለውን ተሰጥኦ መጠቀም ይገባል ብለዋል።

አክለውም እኛ ኢትዮጲያውያን ችለን የተገኘንበትን የጉባ ብስራቶች በሌሎች የልማት ስራዎች መድገም ያስፈልጋል ብለዋል።

የክፍለ ከተማው ብልጽግና ፖርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ምክትልና ፖለቲካ ዘርፉ ኃላፊ አቶ ጎሳ ወርቁ፥ አሰባሳቢ ገዢ የሆነ የወል ትርክት ለመገንባት እኔ ከሚል እኛ ወደሚል እሳቤ በመሻገር ፀጋዎቻችንን በጋራ መጠቀም ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል።

የክፍለ ከተማው ባህል ኪነ-ጥበብ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ አዲሴ ጌትነት ፥በጉባ ላይ ያሳየነውን አርበኝነት ለመድገም አሰባሳቢ በሆኑ የጋራ ትርክቶችን በኪነ ጥበብ እያዋዛን የምንገልጽበት ምሽት ነው ብለዋል።

በመድረኩ አጭር ተውኔት፣ ግጥም እንዲሁም ሌሎች አዝናኝና አስተማሪ የሆኑ የተለያዩ ኪነ-ጥበባዊ ስራዎች ለታዳሚያን ቀርቧል።

የ2018በጀት አመት የመጀመሪያው የ6 ወራት የመንግስት እና የፓርቲ ስራዎች እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በጠቅላላ አመራር ተገመገመ።ዜና ላፍቶ ጥር 1/2018ዓ.ምበንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ...
09/01/2026

የ2018በጀት አመት የመጀመሪያው የ6 ወራት የመንግስት እና የፓርቲ ስራዎች እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በጠቅላላ አመራር ተገመገመ።

ዜና ላፍቶ ጥር 1/2018ዓ.ም

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 አስተዳደር የ2018በጀት አመት የ6 ወራት የመንግስት እና የፓርቲ ስራዎች እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በጠቅላላ አመራር ተገመገመ።

የመንግስት እና የፓርቲ የ6 ወራት ስራዎች እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት የመንግስት የ6 ወራት ስራዎች እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ይድነቃቸው ፈቀደ እና የፓርቲ የ6 ወራት ስራዎች እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ አቶ አለሙ አዳሙ ሪፖርት አቅርበዋል ።

ሪፖርቱን መነሻ በማድረግ በጠቅላላ አመራሩ ሰፊ ውይይት እና ግምገማ ተደርጉዋል።

የወረዳ 12 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሰለሞን ፈንቴ እንደተናገሩት የ2018በጀት አመት በመጀመሪያው 6ወር የመንግስት እና የፓርቲ ስራዎች አፈፃፀም የተሻለ እንደነበር እና አሁንም አመራሩ የተሰጠውን ተልዕኮ በመውሰድ በትኩረት በመያዝ ተግባራትን በተቀናጀ አግባባብ በመስራት ውጤታማ ስራ ማከናወን እና ውጤታማ መሆን ያስፈልጋል ሲሉ ገልፀዋል ፡፡

የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ተሰራ በበኩላቸው አመራሩ በዚህ የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያው የ6ወር የመንግስት እና የፓርቲ ስራዎች አፈፃፀም የጋራ መደረጉ ለቀጣይ የተሻለ ስራ እንዲሰራ ያግዛል በቀጣይም የተሰጠውን ስራ በቅንጅት በመስራት ለህብረተሰቡን ግንዛቤ በመፍጠር የተሻለ ስራ መስራት አለብን ሲሉ ገልፀዋል፡፡

በመጨረሻም የወረዳው ጠቅላላ አመራር ተግባራትን በእኩል በመያዝ እቅዶችን ማሳካት እንደሚገባ በመግለፅ የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ በማስቀመጥ ግምገማዉ ተጠናቋል ።

የባለጉዳይ ቀን አገልግሎት አሰጣጥ ምልከታ ተደረገ። ዜና ላፍቶ ጥር 1/2018 ዓ.ምበንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 አስተዳደር የባለጉዳይ ቀን አገልግሎት አሰጣጥ ምልከታ ተደርጓል...
09/01/2026

የባለጉዳይ ቀን አገልግሎት አሰጣጥ ምልከታ ተደረገ።

ዜና ላፍቶ ጥር 1/2018 ዓ.ም

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 አስተዳደር የባለጉዳይ ቀን አገልግሎት አሰጣጥ ምልከታ ተደርጓል።

በምልከታው በወረዳ አስተዳደሩ ያሉ ሴክተር ተቋማት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ባለጉዳይን የሚያስተናግዱበት አግባብ በምልከታው ታይቷል ።

ሁለንተናዊ ትብብር የኢትዮ-ቻይና አጋርነት የጀርባ አጥንት ነው - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት  ሁለንተናዊ ትብብር የኢትዮ-ቻይና አጋርነት የጀርባ አጥንት ነው አለ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን...
08/01/2026

ሁለንተናዊ ትብብር የኢትዮ-ቻይና አጋርነት የጀርባ አጥንት ነው - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ሁለንተናዊ ትብብር የኢትዮ-ቻይና አጋርነት የጀርባ አጥንት ነው አለ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት።

አገልግሎቱ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ የኢትዮ-ቻይና የንግድ ልውውጥ ከ13 ቢሊየን ዶላር መብለጡን አመላክቷል።

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

ሁለንተናዊ ትብብር የኢትዮ-ቻይና አጋርነት የጀርባ አጥንት ነው። የኢትዮ-ቻይና የንግድ ልውውጡ ከ13 ቢሊየን ዶላር በልጧል።

በኢትዮጵያ እና በቻይና መካከል ያለው የኢኮኖሚ ትብብር ቀጣይነት ባለው መልኩ እያደገ በመምጣቱ በሁሉቱ ሀገራት ያለውን የንግድና ኢንቨስትመንት ፍሰትን በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስፋፋ አድርጓል፡፡

በዚህም የሁለትዮሽ የንግድ ለውውጥ ከ13 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የበለጠ ሲሆን ይህም ቻይና ኢትዮጵያን ዋንኛ የንግድ አጋር በማድርግ ግንኙነቷን እያጠናከረች መሆኑን ማሳያ ነው፡፡ ኢትዮጵያም ከቻይና የምታስገባው ምርት በተጠናቀቀው ዓመት መጀመሪያ ላይ ጭማሪ ያሳየ ሲሆን በመጋቢት ወር ብቻ 1.57 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ደርሷል፡፡ ይህም ከባለፈዉ ዓመት ጋር ሲነጻጸር 22% ጭማሪ አሳይቷል።

የውጭ ቀጥተኛ የኢንቨስትመንት ፍሰትም ጠንካራ ሆኖ የቀጠለ ሲሆን፣ ቻይና በማኑፋክቸሪንግ፣ በመንገድና ሕንጻ ፕሮጀክት ግንባታዎች ላይ በመሰማራት ግንባር ቀደም ሀገር ሆና እየሰራች ነዉ፡፡ የኢትዮጵያን የዲጂታል ጉዞን የሚያፋጥኑ የመሠረተ ልማትና የፋይናንስ ተደራሽነት ማስፋፋት በተለይ ከባቡር ሐዲድ ዝርጋታ፣ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች እስከ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ድረስ የተገኙ ስኬቶች የሁለቱን ሀገራት የኢኮኖሚ አጋርነትን አጠናክሯል፡፡

የኢኮኖሚ ትብብር የዚህ አጋርነት የጀርባ አጥንት ሲሆን፣ በየካቲት 2017 በአዲስ አበባ የተካሄደው የኢትዮ-ቻይና የኢኮኖሚ እና የንግድ ልዉዉጥ መድረክ በኢንቨስትመንት፣ በንግድ እና በአቅርቦት ሰንሰለቶች ላይ ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ይበልጥ ኢንዲጠናክር አድርጓል፡፡

ኢትዮጵያ በዚሁ ዓመት ወደ አዲሱ የዓለም የኢኮኖሚ ጥምረት፣ BRICS+ መቀላቀሏ ለዘመናዊነት እና የቻይናን ጨምሮ ለአለም አቀፍ ገበያዎች ተደራሽ የመሆን እድሎችን አስፍቷል፡፡

ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣዉ የሁለትዮሽ ኢኮኖሚ አጋርነት ለሁለቱም ሀገራት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለዉ ነው፡፡ የኢትዮጵያን የዲጂታል ራዕይ ወሳኝ የሆኑ የካፒታል፣ የቴክኖሎጂ እና የገበያዎች መዳረሻ እንዲትሆን እድል የሚያሰፋ ሲሆን፣ ለቻይና ደግሞ ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ እንደ መግቢያ በር ሆና ታገለግላለች፡፡ በተለይ ከቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ ጋር በማጣጣም የቻይና የረጅም ጊዜ የጋራ ልማት ራዕይን እውን ያደርጋል፡፡

ከዚህ አንጻር የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ፣ የፈረንጆቹን የ2026 አዲሱን ዓመት የውጭ አገር ጉብኝታቸውን በአፍሪካ ለመጀመር ታሕሣሥ 30/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡

ይህ ጉብኝት ቻይና የዓመቱን የመጀመሪያ የዲፕሎማሲ ጉዞ በአፍሪካ አገራት የመጀመር የ36 ዓመታት ረጅም ታሪክ አካል ነዉ፡፡ ጉብኝቱ በተለይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ሶማሊያ፣ ታንዛኒያ እና ሌሶቶን የሚያካትት ሲሆን ይህም ቻይና ለአፍሪካ ቀንድና ለቀሪው የአፍሪካ አገራት የምትሰጠውን ትኩረት ከማመላከት ባሻገር የኢትዮጵያ-ቻይና ግንኙነት ለአፍሪካ-እስያ ትብብር የማዕዘን ድንጋይ ሆኖ እንዲቀጥል የጎላ ድርሻ አለዉ፡፡

ሁለቱ ሀገርት በዛሬው ዕለት በኢኮኖሚ፣ ንግድ፣ መሠረተ ልማት፣ የኃይል አቅርቦት እና ትራንስፖርት ብሎም አዲስ በመፈጠር ላይ ባሉ እንደ ኢ-ኮሜርስ፣ ዲጂታል ኢኮኖሚ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት እና አረንጓዴ ኃይል ልማት ላይ ትብብራችንን ለማጠናከር ተወያይተዋል።

በአጠቃላይ የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ጉብኝት በኢትዮጵያና በቻይና መካከል ያለውን ሁለንተናዊ ስልታዊ የኢኮኒሚ ትብብር አጋርነት ይበልጥ እንደሚያጠናክረውና በቤጂንግ በተካሄደው የቻይና-አፍሪካ ትብብር ፎረም (FOCAC) የተመዘገቡ ስምምነቶችን ወደ ተግባር ለመቀየር ፋይዳው የጎላ እንደሆነ ያመላክታል፡፡

በወረዳ 12 አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያው 6 ወር የመንግስት ስራ አፈፃፀም ተገመገመ።ዜና ላፍቶ ታህሳስ 30/2018 ዓ.ምበንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በወረዳ 12 አስተዳ...
08/01/2026

በወረዳ 12 አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያው 6 ወር የመንግስት ስራ አፈፃፀም ተገመገመ።

ዜና ላፍቶ ታህሳስ 30/2018 ዓ.ም

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በወረዳ 12 አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያው 6 ወር የመንግስት ስራ አፈፃፀም ተገመገመ።

በግምገማ መድረኩ በበጀት ዓመቱ ባለፉት 6 ወራት የተከናወኑ የመንግስት ስራዎች ጥቅል ሪፖርት በጥንካሬና በድክመት በዝርዝር ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

በዚህም ከስራ ዕድል ፈጠራ፣ የሌማት ትሩፋት፣ ከበጎ ፈቃድ አንፃር ቤት እድሳትና መዓድ ማጋራት ፣ አገልግሎት አሰጣጥን ከማሻሻል አኳያ ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተሰሩ የልማት ስራዎችን ከማስቀጠል ፣ ተግባራትን በቴክኖሎጂ ከማስተሳሰር አንፃር፣ከሚዲያ እና ከህዝብ ግንኙነት ስራዎች አኳያ መረጃዎችን ለማህበረሰቡ በወቅቱ ተደራሽ ከማድረግ አኳያ ምን ይመስል እንደነበር፣የተለያዩ መድረኮች ከመፍጠር ፣ የተቋማት እርስበርስ ትስስር በመፍጠር የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት የሄዱበት ርቀት እንዲሁም የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ኢኒሼቲቭ ስራዎች በሆኑት የ6ቱ ግቦች አካል በሆኑት የመቀነስ ግቦች፣ የዜሮ ግቦች፣ የ100 ፐርሰንት ግቦች፣ የእጥፍ ግቦች፣ የ1 ግቦች እና ለውጥ የሚፈልጉ ግቦችን ለማሳካት እየተሰሩ ያሉ ተግባራት እንዲሁም የስራ አከባቢን ምቹ ለማድረግና አገልግሎትን በማዘመን ረገድ የተሻሉ ስራዎች እንደተሰሩ ሪፖርት ከተቋማት የፅ/ቤት ሀላፊዎች ሪፖርት ቀርቦዋል።

የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚና አቶ ሰለሞን ፈንቴ ባለፉት 6 ወራት ከልማት፣ ከመልካም አስተዳደርና አገልግሎት አንፃር እንዲሁም የህብረተሰቡን የኑሮ ደረጃ የሚያሻሽሉ በርካታ ሰው ተኮር ተግባራት የተፈፀሙበት እንደሆነ ገልፀው ጽ/ቤቶች በተሰጣቸው ተግባር እንዲሁም ባገኙት ውጤትና በሰራው ልክ እየተመዘነ የተሄደበት አግባብ የተሻለ መሆኑን ገልፀው በቀሪ ወራት ታቅደው ያልተከናወኑና ዝቅተኛ አፈፃፀም የታየባቸው ተግባራት ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ ጠቅሰው ውጤታማነትን እንደመርህ መያዝ እንደሚገባ ዋና ስራ አስፈፃሚው አመላክተዋል።

የወረዳ 12 ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተምኪን ማህዲ እንደገለፁት በአጠቃላይ ባለፉት ስድስት ወራት የተሰሩ የተቋማት አፈጻጸም በተለይ አመራሩ የተሰጠው ተግባራትን አቀናጅቶ በመስራት ውጤታማ መሆን በተለይ የላቀ አፈጻጸም የተመዘገበባቸው ተግባራት አጠናክሮ መቀጠል አለበት ስሉ ተናግረዋል። በቀጣይም ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ላይ መዋቅሩን በማቀናጀት በቀጣይ ትኩረት በሚያስፈልጉ ሰራዎች ላይ በጊዜ የለኝም መንፈስ መረባረብና ውጤታማ ስራ መስራት እንደሚጠበቅ የትኩረት አቅጣጫ አስቀምጧል።

"በቀሪ ጊዜያት የአፈፃፀም ክፍተት በታየባቸው ተግባራትና ርብርብ በሚሹ ጉዳዮች ላይ ማተኮር ይገባል" ወይዘሮ ካባ መብራቱላፍቶ፣ ታህሳስ፣ 30/2018:- በቀሪ ጊዜያት የአፈፃፀም ክፍተት በታ...
08/01/2026

"በቀሪ ጊዜያት የአፈፃፀም ክፍተት በታየባቸው ተግባራትና ርብርብ በሚሹ ጉዳዮች ላይ ማተኮር ይገባል" ወይዘሮ ካባ መብራቱ

ላፍቶ፣ ታህሳስ፣ 30/2018:- በቀሪ ጊዜያት የአፈፃፀም ክፍተት በታየባቸው ተግባራትና ርብርብ በሚሹ ጉዳዮች ላይ ማተኮር ይገባል ሲሉ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ካባ መብራቱ ገለፁ።

በዛሬው ዕለት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የመንግስት ስራዎች እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሂዷል።

በዕለቱም በክፍለ ከተማው ፕላንና ልማት ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ስራ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

በዚህም በተቋም ግንባታ፣ በአገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማነትና ስታንዳርድ አፈፃፀም፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮችንና ቅሬታዎችን ከመፍታት አኳያ፣ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ካረጋገጡ ኢንሼቲቭ ስራዎች አንፃር በሪፖርቱ ተመላክተዋል።

በተጨማሪም ከስራ እድል ፈጠራ፣ ከሌማት ትሩፋትና ከገበያ ማረጋጋት፣ ከትምህርት፣ ከጤና፣ ከገቢ አሰባሰብ፣ ከፀጥታ ስራ፣ የብዙዋን መገናኛ አውታሮችን ከመጠቀም እንዲሁም ከቅንጅታዊ ስራዎች ጋር በተያያዘ በሪፖርተ ከተዳሰሱት መካከል የሚጠቀሱ ናቸው።

የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ካባ መብራቱ በቀሪ ጊዜያት በእቅድ ተይዘው በአፈፃፀም ወደኋላ የቀሩ ተግባራት ላይ እንዲሁም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡና ርብርብ የሚሹ ጉዳዮችን ቅድሚያ ሰጥቶ በመስራት ተጨባጭ ውጤቶችን ማስመዝገብ ይገባል ብለዋል።

ከተያዙ ግቦች አኳያ በተቋማትም ይሁን በወረዳዎች ላይ የአፈፃፀም ልዩነቶች ያሉ መሆኑን አንስተው ሁሉንም ግቦች በእኩል ደረጃ ተፈፃሚ እንዲሆኑ በማድረግ የህብረተሰቡን የአገልግሎት አሰጣጥ እርካታን ማሳደግ እንደሚገባ ተናግረዋል።

ለዚህም ቅንጅታዊ ስራ የበለጠ አቅም የሚፈጥር በመሆኑ ተቀናጅቶ መስራት እንደሚገባ የገለፁት ወይዘሮ ካባ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢንሼቲቭ የሆኑትን 6ቱን ግቦችም ከመደበኛ ተግባራት ጋር አስተሳስሮ መምራት ይገባል ብለዋል።

የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ድላየሁ ታምሬ መደበኛ ስራዎችንና የንቅናቄ ስራዎችን አቀናጅቶ ለመምራት በተደረገው ጥረት የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ የተቻለ መሆኑን ተናግረዋል።

የሚሰጡ ስልጠናዎችና የሚደረጉ ድጋፍና ክትትሎች ለተቋም ግንባታ ሂደት የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ በሂደቱ የተገኙ ውጤቶችን እየተነተኑ መሄድ እንደሚገባ ጠቅሰው በሁሉም ረገድ ያለው አፈፃፀም አዳጊና ወጥነት ሊኖረው ይገባልም ብለዋል።

 #ላፍቶ በጎነት መንደር
07/01/2026

#ላፍቶ በጎነት መንደር

በልደት(ገና) በዓል ቀን ከቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ጋር በመሆን በሼይካ ፋጢማ ቢን መብሩክ የዐይነ ስውራን ትምህርት ቤት በመገኘት መዓድ ተካፍለናል። ይኽቺን ልዩ ማለዳ በጋራ ማሳለፋች...
07/01/2026

በልደት(ገና) በዓል ቀን ከቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ጋር በመሆን በሼይካ ፋጢማ ቢን መብሩክ የዐይነ ስውራን ትምህርት ቤት በመገኘት መዓድ ተካፍለናል። ይኽቺን ልዩ ማለዳ በጋራ ማሳለፋችን የገናን እውነተኛ መንፈስ ያሳየንም ሆኗል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ከሰው ተኮር ተግባራት አንዱ የሆነው የቤት እድሳት ነዋሪዎችን ከተጎሳቀለ ኑሮ በማላቀቅ ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ነው።"ዜና ላፍቶ ታህሳስ 28/2018 ዓ.ም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተ...
06/01/2026

ከሰው ተኮር ተግባራት አንዱ የሆነው የቤት እድሳት ነዋሪዎችን ከተጎሳቀለ ኑሮ በማላቀቅ ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ነው።"

ዜና ላፍቶ ታህሳስ 28/2018 ዓ.ም

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በወረዳ 12 አስተዳደር ስር የሚገኙ አቅመ ደካማ ነዋሪዎችን ለመደገፍ ባለሀብቶችን ፣ ተቋማትንና ማህበረሰቡን በማስተባበር መጪውን የገና በዓል ምክንያት ሙሉ በሙሉ ፈርሰው በአዲስ መልክ የተገነቡ የ4 የአቅመ ደካማ ነዋሪዎች ቤቶችን ሙሉ ዕድሳት በማጠናቀቅ በዛሬው እለት ለነዋሪዋቹ ተበርክቷል።

በመርሃ ግብሩ የተገአኙት እና መልዕክት ያስተላለፍት የወረዳ 12 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሰለሞን ፈንቴ እንደተናገሩት መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ከሚሰራባቸው ሰው ተኮር ተግባራት አንዱ የሆነው የቤት እድሳት ነዋሪዎችን ከተጎሳቀለ ኑሮ በማላቀቅ ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ነው ያሉ ሴሆን መንግስት የሀገር ባለውለታዎችን፣ አቅመ ደካሞችን ፣ አካል ጉዳተኞችን እና ጧሪ ቀባሪ የሌላቸውን አዛውንቶችን በዘርፍ ብዙ ሰው ተኮር ተግባራት እየደገፈ ይገኛል የቤት እድሳትን ከእነዚህ ተግባራት መካከል አንዱ እና አስተዳዳሩ በትኩረትና በስፋት እየሰራበት የሚገኝ ተግባር ነው በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል ።

የቤት ዕድሳት የተደረገላቸው ነዋሪዎች መንግስት ለአቅመ ደካማ ዜጎች ትኩረት በመስጠት ላደረገላቸው ድጋፍ ምስጋናቸውን በማቅረብ ፤ ቤቶቹ ከመታደሳቸው በፊት በክረምትና በበጋ ወቅቶች የተለያዩ ጉዳቶች ሲፈራረቅባቸው የቆየና ቤቶቹ በአዲስ መልክ ተሰርተው በመተላለፋቸው ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል ።

በመርሃ-ግብሩ አስተዳደሩ የቤት ዕድሳት ለተደረገላቸው ነዋሪዎች በዓሉን ተደስተው እንዲያሳልፉ የበዓል መዋያ ስጦታዎች ተበርክቶላቸዋል ።

ወረዳ አስተዳደሩ ለፀጥታ አካላት የገና በዓል መዋያ የሚሆን የበሬ ስጦታ አበረከተ፡፡ዜና ላፍቶ ታህሳስ 28/2018ዓ.ምየንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 አስተዳደር መጭውን የገና በ...
06/01/2026

ወረዳ አስተዳደሩ ለፀጥታ አካላት የገና በዓል መዋያ የሚሆን የበሬ ስጦታ አበረከተ፡፡

ዜና ላፍቶ ታህሳስ 28/2018ዓ.ም

የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 አስተዳደር መጭውን የገና በዓል አስመልክቶ ለፀጥታ አካላት ለአዲስ አበበ ፓሊስ እና ለፌዴራል ፖሊስ ለበዓል መዋያ የሚሆን የበሬ ስጦታ አበርክቷል፡፡

የወረዳው ሰላም እና ፀጥታ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ይልቃል ተፈራ የህዝባችንን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ሌት ከቀን እየተጉ ላሉ የፀጥታ መዋቅር ሰራተኞች በዓሉን ደስተኛ ሆነው እንዲያሳልፉ ስጦታ ተበርክቷል ሲሉ ገልፀዋል፡፡

አክለውም በዓሉ በሰላም ተከብሮ እንዲያልፍ መላው የፀጥታ መዋቅር 24/7 በንቃት ሰላምና ደህንነታችን እያስጠበቀ እንደሚገኝ ገልፀው ለሰላማችን መረጋጋጥ እየተጉ ያሉ አካላትን ማበረታታት ተገቢ ነው ብለዋል፡፡

Address

Addis Ababa

Telephone

0114199350

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Nifas silk Lafto Woreda 12 Communication Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Nifas silk Lafto Woreda 12 Communication Affairs Office:

Share